ETHIOPIA FIRST
Monday, April 14, 2014
የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ሚና በተመለከተ በኖርዌይ ኦስሎ ሕዝባዊ ውይይት ተካሄደ
ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
በዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት አፕሪል ቅዳሜ 12/2014 በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ተሳትፎ በተመለከተ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተካሄደ:: በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ከኦስሎ እና ከተለያየ ከተማ በመምጣት በስብሰባው ላይ የተገኙ ሲሆን የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ በመሆን ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል::
ሕዝባዊ ስብሠባው በኖሬጅያውያን የሰአተ አቆጣጠር ከቀኑ 15:00 እስከ ምሽቱ 21:00 ሰዓት የተካሄደ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አቢ አማረ በኢትዮጵያ ውስጥ በወያኔ አረመናዊ ስርአት በጭካኔ በግፍ ለተገደሉ እና በተለያዩ አስር ቤቶች በፖለቲካ ኣስተሳስባችው ምክንያት ያለወንጀላች የሚስቃዩ ውድ ኢትዮጵያዊን ወገኖቻችን በማስብ በዚሁ ዘረኛ ቡድን አስቃቂ የኣካል ጉዳት ለተፈጸባቸው ኢትዮጵያዊን የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት በማስደረግ ስብሰባውን አስጀምረውታል::
በመቀጠለም አቶ ዮሀንስ አለሙ የዴምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሊቀመንበር የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸው ስለ ዲምክራሲያዌ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አመሰራረት እና ስለ ድጋፍ ድርጅቱ አላማ በማብራራት የድጋፍ ድርጅቱ በአሁኑ ሰአት በሀገር ቤት በሰላማዊ ትግል የወያኔን መንግስት ለመጣል እየታገሉ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶችን እየረዳ እንደሚገኝ እና ከሀገር ውጭ ደግሞ የወያኔን መንግስት በሁለገብ ትግል ለማስወገድ እየሰራ ያለውን የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ የፖለቲካ ድርጅትን በግንባር ቀደምነት እየረዳ እንዳለ በመግለጽ የወያኔን ዘረኛ ስርአት ለመጣል ሁሉም ሰው አስተዋጿ ማድረግ እንደሚጠበቅበት እና ማንኛውም ኢትዮጵያዌ ዜጋ በሀገራችን የጋራ ጉዳይ ስለሆነው የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ሀሳብ በመለዋወጥ ፣በመካከላችን ያሉትን ማንኛውንም የሃሳብ ልዩነቶች ወደ ኋላ በመጣል ፣ በመቻቻል፣ ሀገር እያፈረሰ እና ሕዝብ እያዋረደ ያለውን የዘረኛውን የወያኔን መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሁለገብ ትግል ለማስወገድ መረባረብ እንዳለበት አጽኖት ሰጥተው ንግግር አድርገዋል::
Ethiopians public meeting in Norway
በመቀጠለም ዲምክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ድጋፍ ከሚሰጣቸው ድርጅቶች መካከል አንዱ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል የሆኑት አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ ሰፊውን ጊዜ በመውሰድ ከንጉሱ ስርአት ጀምሮ በደርግ መንግስት ዘመንም በሀገራችን የተደረጉ የፖለቲካ ንቅናቄዎችንና ለውጦችን አንድ በአንድ በመዘርዘር አሁን ካለው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር በማነጻጸር ሰፋ ያለ ትንታኔ ያቀረቡ ሲሆን አሁን ላይ ሀገሪቱን እየመራው ነው የሚለው የወያኔ መንግስት ከዚህ ቀድሞ ኢትዮጵያን ከመሩት ከሁለቱ መንግስታቶች ማለትም ከንጉሱም ከደርግም መንግስት ጋር ሲነጻጸር ፈጽሞ እንደማይገናኝ የወያኔ መንግስት ዘረኛና የዘረኝነት ፖለቲካ እያራመደ ያለ አረመናዊ መንግስት እንደሆነ አብራርተዋል::
የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ አክለውም ከወያኔ በፊት የነበሩ ሁለቱ መንግስታቶች ለውድቀት የዳረጓቸውን ምክንያቶች በመጥቀስ የወያኔን አንባ ገነናዊ መንግስት ለአፋጣኝ ውድቀት ሊዳርጉት ይችላሉ የሚሉትን ግልጽ ምክንያቶች በመዘርዘር አስቀምጠዋል:: አቶ ቡዙነህ በሁለት የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በማንሳት እና በማብራራ ከሕዝብ ውይይት እንዲያደርጉበት ለመወያያ ያቀረቡ ሲሆን እነዚህም:
1, በሙስሊሙ ማህበረሰብ እና በወያኔ መካከል ያለው ግጭት
2, የህዳሴ ግድብን በማስመልከት ያለው ተቃውሞ
ስለሙስሊሙ ማህበረሰብ ተቃውሞ ሲናገሩ የሙስሊሙ ትግል በሁለት አመታት ውስጥ የተደረገው ሰላማዊ ትግል በጣም የተሳካና ወያኔ በቀላሉ ሊያዳፍነው ያልቻለው ሰላማዊ መብትን የመጠየቅ ትግል እንደሚያደንቁ በመናገር ነገር ይህ በሙስሊም ማህበረሰብ በኩል እየተደረገ ያለው ትግል እስከ አሁን ድረስ ከመንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ሊያገኝ እንዳልቻለ እና ወደፊትም ከወያኔ መንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ያገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል:: ለዚህም ማስረጃው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ከጠየቋቸው አራት የመብት ጥያቄዎች አንዱም ካለመመለሱ በተጨማሪ እስካሁን መሪዎቻቸውም በሃሰት ውንጀላ በእስር እየማቀቁ ያለፍርድ እየተንገላቱ መሆናቸው ነው::
ነገር ገን አሁን እየሆነው ባለው ሁኔታ በእንደዚህ አይነት መንገድ እስከመቼ ድረስ የሙስሌሙ ትግል ይቀጥላል በማለት የተናገሩ ሲሆን አሁን እየሄደ ባለው አካሄድ የሙስሊሙ ተቃውሞ የትግል አቅጣጫውን እስካልቀየረ ድረስ ረጅም ርቀትን ትግሉ ሊቀጥል ይችላል የሚል እምነት እንደሌላቸው እና ነግር ግን የሙስሊሙ ጥያቄ ከእምነት መብት ጥያቄ ባሻገር ወደ የዜግነትን መብት ወደ ማስከበር መለወጥና መሸጋገር እናደለበት በመናገር የሙስሊሙ ማእበረሰብ ጥያቄ ፍሬ ሊያፈራ የሚችለው ትግሉ በዚህ መልኩ ሲቀጥል እንደሆነ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰተዋል::
በሁለተኛም የህዳሴ ግድብ በሚመለከት ያቀረቡት ሀሳብ ወያኔ የራሱን የፖለቲካ ኪሳራና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉን ግፍ በዕድገት ስም ለመሸፈን ያመጣዉ እንጂ ታቅዶበትና ለህዝቡ በማሰብ እንዳልሆነ በኢትዮጵያና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉ ግፍ እንደ ማስረጃነት በማቅረብ ያብራሩ ሲሆን እንደ ምሳሌም ወያኔ ሃገራዊ የሆነ አላማ ይዞ ካለመነሳቱ አንፃር የሃገርን ድንበር አሳልፎ እስከመስጠት እየሄደ ያለበትን ሁኔታ ጠቅሰው ይህ አሰራር ደግሞ የዲክታተሮች ባህሪ እንደሆነ አብራርተዋል::
የወያኔ መንግስት በህዳሴ ግድብ ሰበብ ምክንያት በማድረግ በመላው አለም ኢትዮጵያኖች በሚኖሩበት ሀገሮች በመዞር የዲያስፖራውን ቀልብ ለመውሰድ የሚያደርገው የአባይ ቦንድ ሽያጭ ሩጫ በዲያስፖራ ተቃዋሚዎች አማካኝነት በፍጹም እንዳልተሳካለት ይህንንም የወያኔ በአባይ ቦንድ ሽያጭ ስም ገንዘብ ዘረፋ በመቃወም ወያኔን አሳፍረው ከመለሱት መካከል በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች እንደሆኑ በማስታወስ የዚህ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሰበብ የወያኔን መንግስት ወደ መጥፎ ውድቀት ላይ ሊጥለው እንደሚችል በማመን የወያኔ መንግስት በአሁን ሰአት ከግብጽ መንግስት ጋር እየገባ ያለው ሰጣ ገባ ለኢትዮጵያ መጥፎ ሊሆን እንደሚችል በመግለጽ ንግግራቸውን አጠቃለዋል::
በመቀጠልም አቶ ብዙነህ ባነሷቸው ነጥቦችና እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ለቀረበላቸው በርካታ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጓል፥፥ ከውይይቱም በማስቀጠል የዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ዳንሄል አበበ የዲምክራሲያዌ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የአቋም መግለጫ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ድርጅታቸው ወያኔ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍና በደል ፈጽመው እንደሚያወግዙ እና ዴምክራሲያዌ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሁል ጊዜ ከግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ ጎን እንደሚቆም ቃል በመግባት የአቶ ቡዙነህ ፅጌን በኖርዌይ በመገኛት ለህዝቡ ለሰጡት ገለጻ አመስግነዋል::
በዝግጅቱ መጀመሪያና ማጠቃለያ ላይ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል መዝሙር በመዘምራን የተዘመረ ሲሆን በየጣልቃው የተለያዩ የባህል ዘፈኖች በተወዛዋዦች ታጅቦ የቀረበ ሲሆን ጣእም ያለው ባህላዊ ምግብም በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የሴቶች ክፍል ተስተናግዷል፥፥ ስብሰባውን ተጀምሮ እስኪያልቅ አቶ ፍቅሬ አሰፋ መርተውታል::
በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ለዝግጅቱ መሳካት የበኩላችሁን ላበረከታችሁና ከተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች ረዥም ርቀት በመጓዝ የዝግጅቱ ታዳሚ ለነበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን እና እንዲሁም የድርጅቱ አባላቶች ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
አንድ ባርያ ነጻ የሚወጣው መቼ ነው? ሲፈቅድ ነው? ወይስ ሲፈቀድለት? (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)
በአለፈው ሳምንት (ፋክት ቁጥር 36) ወይዘሮ መስከረም የተለያዩ መጻሕፍትን በመጥቀስ በሴቶች ላይ ያለውን መጥፎ ጫና በደንብ ያስመሰከረች ይመስለኛል፤ ግን እኮ በሴቶች ላይ ያለው ጫና የቆየ፣ ክፉና ጎጂ መሆኑን ማንም ያውቀዋል፤ ቁም-ነገሩ ያለው ከዚያ የባህል ጭነት በራስ ጥረት ወጥቶ፣ ነቀፌታንም ሆነ እርማትን ለመቀበል ሳይፈሩና ሳያፍሩ እንደመስከረም በአደባባይ ሀሳብን በመግለጽ በአገርና በወገን ጉዳይ መሳተፍና ሌሎችም እንዲሳተፉ የተቻለን ሁሉ ማድረጉ ላይ ነው፤ ለዚህ ነው ይህንን መልስ የምጽፈው፤ ወይዘሮ መስከረም በአጋጠሟትና በምታያቸው እንቅፋቶች ላይ ማተኮርዋ እንደርስዋ መንፈሳዊ ወኔው የሌላቸውን ያስፈራራቸዋል እንጂ አያበረታታቸውም፤ የማንንም አፍአዊ ጫና ተቋቁመው በራሳቸው የውስጥ ኃይል እንዲመሩ እናድርግ።Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
አንድ መጽሐፍን በመጥቀስ ወይዘሮ መስከረም የሚከተለውን ጽፋለች፡–
ፈጣሪ የሠራውን ውጫዊ ገጽታን ማሽሞንሞን በቂ እንደሆነ ሲነገራት የኖረች ሴት፣ በምን ተነሳሺነት አእምሮዋን የሚመግብ እውቀት ልትሻ ትችላለች? … በልጅነት እውቀትን ወደመሻት ያልተገፋ ማንነት በጉብዝና ወራት አላዋቂ በመሆን ቢወቀስ ትርጉም አይኖረውም፤ …››
ወይዘሮ መስከረም ሔዋን ሲነገራት የማትሰማ የመጀመሪያዋ ሰው (ልብ በሉ ሴት አላልሁም፤) መሆንዋን እንዴት እስከዛሬ ሳታውቅ ቀረች? ባለመጽሐፉም ይሁን መስከረም የሔዋንን ታሪክ ሳያነሡ መቅረታቸው መሠረታዊ ስሕተት ነው፤ በተጠቀሱት ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ውስጥ አንድም እውነትን የሚመስል ነገር የለም፤ መስከረም ‹‹የሔዋን ዘር›› ከማለት በፊት የሔዋንን ሥራ ቆም ብላ ብታስታውስ የጠቀሰችውን መጽሐፍ እኔ እንደምነቅፈው ትነቅፈው ነበር፤ የሔዋን ታሪክ የሚነግረን የሚከተለውን ነው፡ ‹‹ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደሆነ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፣ ለጥበብም መልካም እንደሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው፤ እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ፤ የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ፤›› ዘፍ. 3
የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ ማለት ‹‹እንደእግዚአብሔር መልካምንና ክፉን የሚያውቁ›› ሆኑ ማለት ነው፤ አሁንም ሔዋን መስከረምና ባለመጽሐፉ እንዳቀለሏት አለመሆንዋን መረዳት ይቻል ነበር፤ እንዲያውም ከዚህ በፊት እንደጻፍሁት ሔዋን የመጀመሪያዋ አብዮተኛና የነጻነት እናት ነች ለማለት ይቻላል! በአንጻሩ አዳም የፍርሃት አባት ነው፤ ‹‹ራቁቴን ስለሆንሁ ፈራሁ፤›› ያለው እሱ ነው! ስለዚህ ወይዘሮ መስከረም ‹‹የሔዋን ዘር›› የምትለውን በድላለችና ይቅርታ መጠየቅ ሳያስፈልጋት አይቀርም!
ሔዋን የተጠቀመችው ውጫዊ ገጽታን የሚያሽሞነሙን ሳይሆን የውስጥን የመንፈስ ኃይል ቆፍሮ በማውጣት ነበር፤ በዚህ የውስጥ ኃይል ለሚጠቀም ከውጭ ግፊት አይጠብቅም።
‹‹እውቀትን ወደመሻት ያልተገፋ ማንነት›› አይወቀስም፤ ትላለች ወይዘሮ መስከረም፤ እየተገፉ የሚገኘው ባርነት ነው፤ እውቀት የሚገኘው በነጻነት ነው፤ መገፋት ከእውቀት ያርቃል እንጂ ወደእውቀት አያስቀርብም፤ የመስከረም ዋናው መልእክት ሰላቢውን እንጂ ሰለባውን አትውቀስ የሚል ነው፣ ወይም የኔ ሀሳብ አህያውን ፈርቶ ዳውላውን ዓይነት ሆኖባታል፤ ለመሆኑ ሰለባ የሚሆን ከሌለ ሰላቢ ይኖራል ወይ? ሰለባ ከመሆን በፊት ሰለባ ላለመሆን መጣር አንዱ የኑሮ ዓላማ አይሆንም ወይ? ከዚህ በፊት ስለጨቋኝና ተጨቋኝ ደጋግሜ ጽፌ ነበር፤ ጭቆና የጨቋኙ ባሕርይ የሚሆነውን ያህል የተጨቋኙም ባሕርይ ይሆናል፤ ለጨቋኙ ጭቆና የሚጠቅመውን ያህል ለተጨቋኙም ጭቆና ይጠቅመዋል፤ ለጨቋኙ ጭቆና የኑሮው መሠረት የሆነውን ያህል ለሚርመሰመሱት የጨቋኝ ሎሌዎች ጭቆና የኑሮ መሠረታቸው ነው፤ እንዲህ እያለ ወርዶ ወርዶ የጭቆና ጠቃሚነት ለሎሌው ሎሌ፣ ለሎሌው ሎሌ ሎሌ … በኢትዮጵያ ምናልባትም የመጨረሻዋ የጭቆና ሰለባ ሚስት ትሆናለች፤ ወይም ልጆች ይሆናሉ! ጨቋኝና ተጨቋኝ የባሕርይ ቁርኝት አላቸው፤ አንዱ ያላንዱ አይኖርም፤ ወይዘሮ መስከረም ይህ እውነት ያልሆነበት ሁኔታ ወይም አጋጣሚ የምታውቀው ካለ ብታጋራን ደስ ይለኛል፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፤›› የሚለው ኢየሱስ ክርስቶስ የሞቱትንና በቁማቸው የሞቱትን ሲያመሳስላቸው ነው! ለእኔ የሚታየኝ እንዲህ ነው።
መስከረም ብዙ ታላላቅ ሴቶችን ጠቅሳለች፤ በእስዋ ግምት ሁሉም በአባታቸው ወይም በባላቸው እየተገፉ ወደትልቅነት መድረኩ የወጡ ናቸው፤ አዙራ ብታየው የጠቀሰቻቸውን ሴቶች ገፉ የምትላቸው ወንዶች መጀመሪያውኑ በሴቶቹ ተገፍተው እንደነበረስ ሊታሰብ አይገባም? ምናልባት ከጠቀሰቻቸው ሴቶች ይልቅ መስከረም የሄለን ኬለርን ታሪክ ብታስታውስ ኖሮ መገፋትን አታነሣም ነበር፤ ሄለን ኬለር በሕጻንነትዋ ዓይኖችዋም ጆሮዎችዋም ሥራቸውን አቆሙ፤ የሄለን ኬለር የመንፈስ ጥንካሬ ከውስጥዋ አዲስና የተሻሉ ዓይኖችንና ጆሮዎችን እንድታበቅልና እንድትማር፣ ከታወቀ ዩኒቨርሲቲም የመጀመሪያዋ ሴት ምሩቅ ለመሆን እንድትበቃ አድርጓታል፤ ይህች አስደናቂ ሴት ከመቶ ሠላሳ ዓመታት ግድም በፊት ማኅበረሰቡ በሴቶች ላይ የነበረውን አጥር ሰብራ፣ ዓይኖችዋ ባለማየታቸውና ጆሮዎችዋ ባለመስማታቸው የገጠማትን እክል አሸንፋ ራስዋን ከወንዶች በላይ ለማድረግ በቅታለች።
መገፋትን የሚፈልግ ሁሉ፣ ካልገፉት የማይነቃነቅ ሁሉ፣ ሬትን ሲግቱት ይጣፍጣል እያለ የተቀበለ ሁሉ፣ ዶሮ ማታ፣ ዶሮ ማታ፣ እያሉ አታልለው እንኳን ዶሮ የለም ሹሮ ሲሉት የማይናደድ ሁሉ፣ ምኞቱ ልደግ ልመንደግ እያለ ሲነዘንዘው በአፈና ጭጭ የሚል ሁሉ ለወቀሳ ብቻ አይደለም ለውርደትም ክፍት ነው፤ ስለዚህም ተወቅሶ ከውርደት ከዳነ ወቀሳው ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ማለት ነው፤ ዞሮ ዞሮ የሰው ልጆች ሁሉ — ሴት፣ ወንድ፣ ወጣት ሽማግሌ-አሮጊት፣ ባለሥልጣን ተራ፣ ገበሬ ነጋዴ፣ ወታደር ፖሊስ፣ አስተማሪ አስተዳዳሪ፣ ዳኛ ጠበቃ፣ ሀኪም መሀንዲስ፣ … — የፈለገውን ቢሆን ላለበት ሁኔታ ኃላፊነቱ የራሱና የግሉ ነው፤ ራሱን የሚገነባው ወይም ራሱን የሚንደው ራሱ ነው፤ ሰበብ እየፈለጉ ከዚህ ኃላፊነት መውጣት ቀላል ቢመስልም ተመልሶ እምቦጭ ነው፤ ዳገቱን ለመውጣት የሚመረውን እውነት መቀበል ያሻል።
በመጨረሻም በማናቸውም መንገድ፣ በማናቸውም ጊዜ፣ በየትኛውም ቦታ ወደቁልቁለት የሚገፉትን ወይም የሚነዱትን ‹‹እምቢ!›› ብሎ ድምጹን ያላሰማ ገደል ገብቶ ሲንፈራፈር ከራሱ በቀር የሚወቅሰው የለም፤ አቅመ-ቢስነት ከውጭ አይመጣም።
Friday, April 11, 2014
በኢትዮጵያ የመብቶች ትግሎች ሁሉ ህወሓትን ከሥልጣን ወደ ማስወገድ አቅጣጫ ያመራሉ!!!
የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች የክስ ሂደት በበርካታ አሳዛኝ ጉዳዮች የታጀቡ ቢሆኑም የሚሰጡት ትምህርት ግን ከፍተኛ ነው። እነዚህ ወገኖቻችን “ችሎት” በተሰኘው የአገዛዙ የድራማ መድረግ በመገኘት ፍትህን ለመግደል ካባ ለብሰው “ዳኞች” ተብለው ለተኮፈሱ የአገዛዙ ተላላኪ ካድሬዎች እና ለመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ያደረጓቸው ጠንከር ያሉ ንግግሮች ካድሬ “ዳኞችን” አሳፍረዋል፤ ኢትዮጵያዊያንን ግን አኩርተዋል። እኚህ ወገኖቻችን ከወያኔ ችሎት ፍትህ ይገኛል የሚል ብዥታ ባይኖራቸውም መድረኩን መልዕክት ለማስተላለፊያነት ተጠቅመውበታል። በዚሁ መድረክ በአገዛዙ እጅ ከወደቁበት ጊዜ ጀምሮ እየደረባቸው ስላለው ሰቆቃ ሲናገሩ አድማጮች ሊቆጣጥሩት የማይችሉት ሐዘንና እልህ ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል።
ወያኔ እንዲህ ዓይነቱ ጭካኔ የሚፈጽመው በሙስሊም መሪዎች ላይ ብቻ አይደለም። የህግ እውቅና የተሰጣቸው መብቶቻቸው እንዲከበርላቸው በጠየቁ ወገኖቻችን ሁሉ ተመሳሳይ ሰቆቃ ሲፈጸም ኖሯል፤ አሁን እየተፈጸመ ነው። “ኑሮ ከበደን” ያሉ ወጣቶች ተደብድበዋል። “የእርሻ መሬት አጣን” ያሉ ገበሬዎች ከያዙት ቁራሽ መሬት ተፈናቅለዋል፣ ተግዘዋል፣ ከነልጆቻቸው ለጎዳና ኑሮ ተዳርገዋል። በሀረር እና በአዲስ አበባ ከተሞች እንደታየው “ነግደን እንኑር” ባሉ ነጋዴዎች ላይ ከአቅም በላይ ከሆነ ግብር ጀምሮ በንብረታቸው ላይ እሳት እስከመልቀቅ የደረሰ አረመኔዓዊ ድርጊት ተፈጽሟል።
በዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ 18 መሠረት እያንዳንዱ ሰው በግሉም ሆነ በጋራ የፈለገውን ሃይማኖት የመከተልና የማስተማር፤ ያልፈለገውን ደግሞ የመተው መብት አለው። ስለሆነም የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ተግባራት በዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ እውቅና ለተሰጣቸው መብቶቻቸው መከበር ያደረጉት ትግል ነው። ለወጉ ያህል “ሕገ መንግሥት” ተብሎ በሚጠራው ኢትዮጵያዊያንን ለመክሰሻነት ብቻ በሥራ ላይ በሚወለው ሰነድ ውስጥ የተካተቱ ቢሆንም ዓለምዓቀፍ እውቅና ያገኙ መብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ተረግጠዋል። ለእነዚህ መብቶች መከበር በጽናት የቆሙ የኢትዮጵያ ውድ ልጆች ከተራ የመንደር ካድሬና ጆሮ ጠቢ እስከ እስከ ከፍተኛው እርከን ባለ ባለሥልጣኖች ተዋክበዋል፤ ሰቆቃ ተፈጽሞባቸዋል።
ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ለእምነት መብቶቹ መከበር እስካሁን ያደረገው ተጋድሎ የሚደነቅ ነው። የተቀናጁ እንቅስቃሴዎቹ፣ ተምሳሌታዊ የተቃውሞ ምልክቶች አጠቃቀሙ የሚያበረታታ ነው። ክርስቲያኑ ከዚህ የሚማራቸው በርካታ ቁም ነገሮች አሉ።
ከሙስሊም እንቅስቃሴና ወያኔ ይህንን እንቅስቃሴ ለማፈን እየሰዳቸው ካሉ እርምጃዎች የምንረዳው አንድ ትልቅ ሐቅ የቱን ያህል ጨዋና የሰለጠነ ቢሆን ወያኔ የሕዝብ ድምጽ ለማዳመጥ ፍላጎት የሌለው መሆኑን ነው። ሙስሊም ወገኖቻችን ጥያቄዎቻቸውን በሚያስገርም ቁጥብ ሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) ቢያቀርቡም ከወያኔ የተሰጠው ምላሽ ግን አፈና፣ ረገጣ፣ ቶርቸር እና ከእስከዛሬዎቹ ይበልጥ አፋኝ የሆኑ ደንቦችና ድንጋጌዎችን ነው። ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ያደረጓቸው ትግሎችም እንደዚሁ ወደ ባሱ የመብት ጥሰቶች እያመሩ ነው። ከዚህ የምንማረው ነገር ትግሉ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂዎችን መፈተሽ እንደሚያስፈልግ ነው።
እንደሚታወቀው፤ ሰብዓዊ መብቶች እርስ በርሳቸው የተቆራኙ፤ እርስ በርሳቸውም የሚደጋገፉ ናቸው። አንዱ የመብት ዓይነት ሲጓደል፤ ሌላውም አብሮ ይጓደላል። ለምላሴ የመናገር መብት ተገፎ እያለ የማምለክ መብት ሊፋፋ አይችልም፤ ወይም ደግሞ ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት መብት ተጥሶ እያለ የማምለክ መብትን የሚያስከብር ተቋም ሊኖር አይችልም።
ለመብቶች መከበር የሚደረጉ ትግሎች፤ በተለይም ደግሞ የሙስሊም ወገኖቻችን ትግል የደረሰበት ደረጃ በአንክሮ ሲጤን ስትራቴጂን በተመለከተ በጥልቀት ልናስብባቸው የሚገቡ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውን እንገነዘባለን። ለጊዜው ሁለት ነገሮች ላይ አጽንዖት ሰጥተን እናልፋለን።
ከላይ እንደተገለፀው የመብት ትግሎች ሁሉ መደጋገፍ ይኖርባቸዋል። ቀደም ሲል በባህርዳር፣ በኋላም በአዲስ አበባ በሴቶች ዓለም ዓቀፍ ቀን አሁን ደግሞ በደሴ ውስጥ እንደታየው የመብት ጥያቄዎች ሁሉ ተደጋግፈው መነሳት ይኖርባቸዋል። ይህ የመደጋገፍ ልምድ የሁለቱ ትላልቅ ሃይማኖቶች ተከታዮች ለየእምነቶቻቸው ነፃነት በሚያደርጉት ትግል ውስጥ መኖር ይኖርበታል። የሙስሊሞች የመብት ጥያቄዎች የክርስቲያኖችም፤ የክርስቲያኖች ደግሞ የሙስሊሞችም መሆን ይኖርበታል።
በሥልጣን ላይ ያለው የህወሓት አገዛዝ አንዱንም የመብት ጥያቄ መመለስ የማይችል መሆኑ ግልጽ መሆን ይኖርበታል። በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የመብት ጥያቄዎች ግብ ወያኔን ከሥልጣን ከማባረር ያነሰ መሆን አይችሉም። ስለሆነም የመብት ማስከበር ትግል ስናካሂድ ይህን አልመን እና ለዚህም ተዘጋጅተን መሆን ይኖርበታል። ይህ ደግሞ ከፍተኛ የስነልቦና፣ የድርጅትና የስልት ዝግጅት ይጠይቃል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
Monday, April 7, 2014
ያልዘሩትን ማጨድ ከቶ አይቻልም!
የወያኔ መንግስት የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች አጋጭቶ በመካከላቸው ጥርጣሬና መፈራራት አንግሶና የታሪክ ጠባሳዎችን እንደ አዲስ በመጓጐጥ እያደማ ከፋፍሎ ለመግዛት ካለመታከት ያደረጋቸው ሙከራዎች ገና ፍሬ ባያፈሩም ቁጥቋጦዎቹ መብቀል ጀምረዋል። እዚህም እዚያም በካድሬዎች የውስጥ ለውስጥ ተልእኮ የሚለኮሱ እሳቶች መብለጭለጭ ጀምረዋል። ሌላው ቀርቶ በአንድ ብሄረሰብ መሃል ሳይቀር በከባቢ ልዩነቶች ብቻ መናቆሮችና መጋደሎች እያስተዋልን ነው። ሰሞኑን በጉጂና በቦረና ኦሮሞዎች መካከል የወያኔ ሎሌዎች በሚያበረታቱት አተካሮ የብዙ ወገኖቻችን ህይወት ጠፍቷል። ሰዎች ከኑሮአቸው ተፈናቅለዋል። ወያኔ እንደኳስ ጨዋታ ተመልካች ዳር ሆኖ ይመለከታል፣ ያጨብጭባል።
ሰሞኑን ባህርዳር ከተማ ውስጥ በተካሄደ የስፖርት ውድድር ላይ አሳፋሪ ክስተት ነበር። ለሰሚው የሚቀፍ ብልግና የተቀላቀለበት ስድብና ቁርቋሶ አይተናል። ከበስተጀርባ ሆነው ይህንን ለፍቅር ብቻ ሊውል የሚገባ የስፖርት ዝግጅት መርዝ ረጭተውበታል። ከዚህ ላቅ ያሉ የተንኮል ድግሶችም ተደግሰው ህዝብ ውስጥ በወያኔ ከተነዙ የመርዝ ቢልቃቶች ውስጥ ስራ ላይ ሳይውሉ ቀርተዋል።
ይህ በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅ ዘር የሚዘራው ወያኔ ያልተከፋፈለ ህዝብ አይገዛልኝም በሚል ፍልስፍና እንደሆነ በተደጋጋሚ እያየን ነው። ሶማሌ ክልል ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ ፖሊስ በሚል ስያሜ በሚጠሩ የመንግስት ሃይሎች ጥቃት ቁጥሩ እጅግ በርካታ የሆነ የኦሮሞ ማህበረሰብ ከኖረበት መሬት ተጠራርጎ እንዲወጣ ተደርጓል። ብዙዎቹ ተገድለዋል። ብዙ ደም መቃበት ተፈጥሯል። በየክልሉ ምስኪን የአማራ ገበሬዎችን መሬት ንብረት በመንጠቅ አከባቢውን ለቀው እንዲሄዱ አድርገዋል። መሄጃ የለንም ያሉትንም ቀጥቅጠው እንደገደሏቸው ሰሞኑን ከጅባትና ሜጫ አካባቢ ያሉ መረጃዎችን አይተናል።
እነዚህ በየቦታው የሚብለጨለጩ እሳቶች በዚህ ከቀጠሉ ሁላችንም ወደ ሚያቃጥልና የሚለበልብ የሰደድ እሳት ማደጉ አይቀርም። የወያኔ ባለሟሎች ካለምንም ይሉኝታና ማሰላሰል ይህንን እሳት እያራገቡ ይገኛሉ።
ይህንን አደገኛ አዝማሚያ በንጭጩ ማስወገድ የሚችለው ራሱ ህዝቡና የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ የነጻነት ሃይሎች ድምጽና ህብረት እንጂ የወያኔ መንግስት አይደለም። ስለዚህ ህዝቡ በተለይም ወጣቶች ከዚህ ወጥመድ ሰብረው እንዲወጡ ግንቦት 7 የነጻነት፣ የፍትህና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አጥብቆ ያሳስባል። ተመሳሳይ ተንኮሎችንም ማጋለጡን ይቀጥላል። የብሄርሰብ ልሂቃንም ይህንን መርዝ እንዲቋቋሙ፣ ይልቁንም ወያኔ እንዳይመቸው ይበልጥ መቀራረብና ፈተናውን በጋራ እንድንቋቋም ጥሪያችን በድጋሜ እናቀርባለን።
ያልተዘራ አይታጨድም። ወያኔ የዘራልን መርዝ የሚያፈራው መርዝን እንጂ ሌላ አይደለም። ልዩነቶቻችን እንደዘመኑ በሰለጠነ ዲሞክራሲያዊ መንገድ እንጂ በተያዘው መንገድ ማስወገድ አይቻልም።
ዞሮ ዞሮ በዚህ ሳይጣናዊ የወያኔ መሰሪ ሴራ ለምትፈስ ለእያንዳንዶ የደም ጠብታ ተጠያቂው የወያኔ ጉጅሌ መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን። በመሆኑም ለመከፋፈል ከመመቻቸት ይልቅ አንድነታችን በማጥበቅ የነጻነት ሃይሎችን በመቀላቀል ራሳችን እና የሀገራችንን ህልውና ከዚህ ከወያኔ የመከፋፈል መርዝ እንታደግ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
Thursday, April 3, 2014
ኢህአዴግ የአፍሪካ ቀንድ ስጋት?
አሜሪካ መለስ ከቆፈሩት ጉድጓድ ለመውጣት ወስናለች
ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም ብቸኛ ተዋናይና ፊት አውራሪ አድርጎ ራሱን የሾመው ኢህአዴግ ለቀጠናው ስጋት እንደሚሆን ተጠቆመ። አልሸባብንና አልቃይዳን ከምንጩ እናጠፋለን በሚል ስትራቴጂ መለስ ከቆፈሩት ጉድጓድ ውስጥ ሰምጣ የነበረችው አሜሪካ ከጉድጓዱ ለመውጣት ወስናለች። ኢትዮጵያዊያን የሚያምኑትና የሚቀበሉትን መሪ በድፍረት አደባባይ የማውጣት ሃላፊነቱ “አገር ወዳድ” በሚሉ ዜጎችና የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጫንቃ ላይ ነው።
ህወሃት ያቋቋማቸው ጥቃቅን መንግስታት ከህዝብ ይልቅ ለህወሃት የወደፊት እቅድ ታማኝ በመሆን መጓዛቸው ከቀን ወደቅን የፈጠረው ስሜት ኢህአዴግን እየበላው እንደሆነ የጠቆሙ የዜናው ምንጮች፣ ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪቃ የሰላም አባት ሊሆን ቀርቶ የራሱንም ችግር መፍታት ወደማይችልበት የቁርሾ ማሳ ውስጥ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
ህወሃት “በነጻ አውጪነት” ያሰላውና፣ ይህንኑ ዓላማውን በፈለገበት ቀን ተግባራዊ ለማድረግ ያመቸው ዘንድ በየክልሉ ለጣጥፎ ያቋቋማቸውን ፓርቲዎች ሲመሩ የነበሩት አቶ መለስ በድንገት ካለፉ በኋላ ኢህአዴግ ውስጣዊ ሰላሙ መናጋቱ በተደጋጋሚ እየተገለጸ ነው። ኢህአዴግ በበኩሉ “የጓድ መለስን ውርስና ራዕይ ያለማዛነፍ እናስቀጥላለን” እያለ አገሪቱን በደቦ እንድተመራ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
አቶ መለስ በጓዶቻቸው ቋንቋ “ተሰው” ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ምክትል ጠ/ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝን ለመተካት ተቸግሮ ነበር። ደህንነቱን፣ መከላከያውን፣ ፖሊስና ዋንኛ የአገሪቱን ተቋማት ጠቅልሎ የያዘው ህወሃት በቀጥታ አሜሪካ ባደረገችው ጫና ሳይወድ በግዱ አቶ ሃይለማርያምን በጠ/ሚኒስትርነት ለመሰየም ተገደደ። የስልጣን ክፍተቱን በተመለከተ አቻ ድርጅቶችና ህወሃት ውስጥ አለመግባባት ተፈጥሮ ስለነበር “ምደባ” በሚል ኢትዮጵያ በደቦ የሚመሯት አራት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተሰየሙላት።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የአሜሪካ ዲፕሎማት እንዳሉት አሜሪካ ስጋት የገባት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነበር። መለስ እንዳለፉ ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ በመላክ ሁኔታውን በመገምገም ስራ የጀመረችው አሜሪካ አሁን አሁን በህወሃት ስትራቴጂ የተሰራው ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ዋንኛ የችግር ምንጭ ስለመሆኑ ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል። በዚህም የተነሳ የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየመከሩበትና የመፍትሔ ስትራቴጂ እየነደፉ ነው።
“We cannot afford to lose Ethiopia” አሜሪካ ኢትዮጵያን ልታጣት አይገባም በማለት ለጎልጉል የዋሽንግቶን ዘጋቢ የተናገሩት የዲፕሎማት ምንጭ “የአሜሪካን ባለስልጣናት ኢህአዴግን በተመለከተ የሚጠቀሙት ቃልና የድምጻቸው ቃና ተቀይሯል” ሲሉ የጉዳዩን ክብደት አመላክተዋል።
በዋሽንግቶን የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የምክር ቤት አባላት እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው ኢህአዴግን አስመልክቶ ተደጋጋሚ ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል። አዲስ አበባም ተወካይ በመላክ ከሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጋር በግል እየተነጋገሩ ነው። በያዝነው ሳምንትም ለተመሳሳይ ስራ አዲስ አበባ የተጓዙ አሉ። እንደ ዲፕሎማቱ ገለጻ የህወሃት ሰዎች ውስጣዊ ችግር እንዳለ አይቀበሉም። በግል ያነጋገሯቸው የሌሎች ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ግን ኢህአዴግ ውስጡ አለመረጋጋትና ስጋት የተሞላው ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
በኢትዮጵያ አንድ ችግር ቢፈጠር ለማረጋጋት አስቸጋሪ እንደሚሆን፣ ህዝቡ በተለይ በህወሃቶች ላይ የሚያሳየው ጥላቻ እየተካረረ መምጣቱ፣ በአገሪቱ የሚፈጸመው ያልተመጣጠነ የሃብት ስርጭት፣ አፈናውና ሌሎች የህወሃት/ኢህአዴግ ተግባራት ተዳምረው ህዝቡን ክፉኛ ማስቀየሙ ያልታሰበ ችግር ሊቀሰቅስ እንደሚችል አሜሪካ መገንዘቧን ያወሱት ዲፕሎማት፣ “ህወሀቶች የቀጠናው የሰላም ምንጮች ስለመሆናቸው ለራሳቸው ምስክርነት ለመስጠት ቢሞክሩም በተግባር የሚታየው ግልባጩ ነው” ብለዋል።
ኢትዮጵያ ላይ የተተከለው የጎሳ አገዛዝ እንደሆነ ያመለከቱት እኚሁ ዲፕሎማት “በጎሳ አስተሳሰብ የተዋቀረው ኢህአዴግ ችግሩ ከገነፈለ ሊቆጣጠረው የሚችል ባለስልጣንና መሪ የለውም። አስተዳዳራዊ ማዕከላዊነት አይታይበትም። በግል የሚወስን ባለስልጣንና ርምጃ የሚወስድ አካል የለውም” ሲሉ የስጋቱን ግዝፈት ያሳያሉ። በዚህ ሂደት ውስጥ ችግሩ ቢከሰት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሰቡ አዳጋች እንደማይሆን ይጠቁማሉ። አያይዘውም “አሜሪካ ቸል ብላ ስትመለከተው የነበረውን ጉዳይ አጽንኦት ብትሰጠው አይገርምም” ብለዋል። አሜሪካ ይህንን የምታደርገው ለራሷ ስትል እንደሆነ ያልሸሸጉት ዲፕሎማት አንድ ጥያቄም ጠይቀዋል። “እናንተስ ለራሳችሁ ስትሉ ምን እየሰራችሁ ነው?” ከረጅም ፈገግታ ጋር።
አልቃይዳን ከምንጩ ማድረቅ በሚለው የመለስ ስትራቴጂ ለኢህአዴግ ግብር ስታስገባ የነበረችው አሜሪካ ግብሯን ስትገብር የኖረችው በፔንታጎን ወታደራዊ ውሳኔ መሰረት ነበር። ኢህአዴግም ግብሩ እንዳይቆምበት በአዲስ አበባ ታክሲ ላይና ህዝብ በሚያዘወትርባቸው ቦታዎች ፈንጂ በማፈንዳት ሲጫወተው የነበረውን ድራማ ዊኪሊክስ (ሹልክ ዓምድ) አምባሳደር ያማማቶን ጠቅሶ ማጋለጡ አይዘነጋም። በዚሁ መነሻ ይመስላል ኢህአዴግ የቀድሞውን ጨዋታ የመጫወት እድሉ እንዳከተመ እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ባደባባይ የመለስን ስብዕና በመዝለፍ ባልተለመደ መልኩ ተናግረው ነበር።
ለጎልጉል መረጃ የሰጡት ዲፕሎማት “እናንተስ” በሚል ለሰነዘሩት ጥያቄ ማብራሪያ ተጠይቀው “እኔ ኢትዮጵያዊ ብሆን አገሬን አስቀድማለሁ” የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል። አሜሪካ አማራጭ ማጣቷንም እንደ አንድ ችግር አንስተዋል።
በዲፕሎማቱ አስተያየት ላይ ገለልተኛ ወገኖችን አነጋግረናል። ያሰባሰባንቸው አስተያየቶች “አሜሪካ እዚህ ደረጃ ከደረሰች፣ ኢህአዴግም በዚህ ደረጃ ከተመደበ ተቃዋሚዎች የግል ጉዳያቸውንና ፕሮግራማቸውን ለህዝብ ውሳኔ በመተው ለመጪው ትውልድና ለአገር ሲሉ ከመቧደን በሽታ ሊፈወሱ ይገባል” የሚል ይገኝበታል።
የተቃዋሚ ፓርቲዎች ተቀናጅቶ መበተን፣ ተደራጅቶ መፍረክረክ፣ ተደላድለው መስለል በተለያዩ ወቅቶች ህዝብ ተስፋ እንዲቆርጥ አድርገዋል። የሚፎካከሩትን ፓርቲ ትተው እርስ በርሳቸው ለተራ ጉዳይ ሲሻኮቱ ዓመታት አሳልፈዋል። በዚህም የተነሳ “አማራጭ የለም” በሚል ኢህአዴግን ማንገስ ግድ እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪዎች “የተቃዋሚ ፓርቲዎች ይህንን አስተሳሰብ ሰብረው አገር መምራት እንደሚችሉ የሚያረጋግጥ ህብረት መፍጠር ይገባቸዋል። ይህም ካልሆነ የርስ በርስ ውዝግባቸውን ማቆምና የራሳቸውን የቤት ስራ መስራት ላይ ማተኮር ግዳጃቸው ይሆናል” ብለዋል።
ምሁራን ከተደበቁበት ሊወጡ እንደሚገቡም ያሳሰቡ አሉ። አገር የመምራት፣ በህዝብ የመታመን፣ የህዝብን ይሁንታ ማግኘት እንችላለን የሚሉ ከፊት ለፊት፣ አሁን ከፊት ያለውን ችግር በመጥረግ የወደፊቷን ኢትዮጵያ በመገንባትና መጪውን ትውልድ በማዳኑ ስራ አጋዥ ሃይል ለመሆን መወሰን እንደሚገባቸው በመግለጽ ጥሪ አቅርበዋል። ከሁሉም በላይ ግን “አሁን ካለው ህዝብን ካገለለ ዘመናዊ የመሳፍንት ስርዓት ኢትዮጵያንና ህዝቧን ማሻገር የሚችል ሞገሰ ሙሉ፣ ቅን፣ ከጥላቻ የጸዳ፣ ከሥልጣን ይልቅ የወደፊቷን ኢትዮጵያ አሻግሮ መመልከት የሚችል መሪ ወደ ፊት ወጥቶ በግልጽ ለህዝብ የሚተዋወቅበትን መንገድ የማህበራዊ ሚዲያዎች፣ ድረገጾች፣ ሬዲዮኖች አገር ወዳድ የመገናኛ አውታሮች አጀንዳ አድርገው ሊወያዩበት ይገባል” የሚለው አስተያየት ሚዛኑን የደፋ ሆኗል።
Wednesday, April 2, 2014
ኢትዮጵያ ውስጥ የመገንጠል ጥያቄ ማንሳት ይቻላልን?
ይህንን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት በቅድሚያ ሀገር ማለት ራሱ ምን ማለት ነው? እንዴትስ ትፈጠራለች? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ይኖርብናል፡፡ ሀገር ማለት በአንድ ጥላ ስር የሚኖርባት ትልቅ ቤት ማለት ናት፣ ሀገር ማለት ጋርዮሽ ማለት ናት፣ ሀገር ማለት ከመንደር ከቀየ የገዘፈች የጋራ ጥቅም የፈጠሩ ሕዝቦች የራሳችን የግላችን የሚሉት የተከለለ ምድርና በውስጡ ያሉ ሁሉ ነገሮች ማለት ናት፡፡
ሀገር እንዴት ትፈጠራለች?
ሀገር በሦስት መንገድ ትፈጠራለች
የተለያየ ቋንቋ ባሕል ሃይማኖት ወዘተ ያላቸው ሕዝቦች በመልክአ ምድር አቀማመጥ በአየር ንብረት መመሳሰልና ተጽዕኖ ሊጋሩት በሚፈልጉት ወይም በሚገደዱት የተፈጥሮ ሀብት አጣማሪነት በስምምነት ትፈጠራለች፡፡
የጋራ ጥቅም ባላቸው ወይም በፈጠሩ አንድ ዓይነት ቋንቋ ባሕል ሃይማኖት ወዘተ ባለው ሕዝብ ያንን የጋራ ጥቅም ለራሳቸው ብቻ ለመጠቀምና ከሌሎች ለመከላከል ባላቸው ጽኑ ፍላጐት ትፈጠራለች፡፡
በኃያላን ገዥዎች ወይም ብሔረሰቦች ፍላጎት አቅማቸው በፈቀደላቸው መጠን ጥቅማቸውን ለማስከበር ለራሳቸው ለማድረግ በጣሩት መጠን ልክ ትፈጠራለች፡፡
እንግዲህ በዓለማችን ያሉ ሀገራት በዚህ መልኩ ሲፈጠሩ በተፈጠሩበት መልክም እንደገና ከውስጣቸውም ሌላ ሀገር ሲፈጠር ማለት እየፈረሱ ሲሠሩ አሁን ካሉበት ደረጃ ደርሰዋል፡፡ ከሀገራት መፈጠር የሚቀድመው ግን የጎጥ መፈጠር ነው፡፡ ፍላጎትና አቅም ከጎጥ ሲያልፍና አስተሳሰብ እየሰፋ እየጎለመሰ ሲሄድ ጎጥ ትጠበዋለች በሂደቱም ሀገር ትወለዳለች፡፡ በመሆኑም ሀገር የሥልጣኔ ፍሬ ናት ማለት ነው፡፡ የሆነ ሆኖ እንደ ዓለማዊ ተረክ ከሰው ልጅ ታሪክ አንፃር ካየነው ሀሳቡ ከ 10ሽዎች ዓታት በፊት የነበረ ሆኖም (አንድ ዓይነት ዝርያ ያላቸው ኅብረተሰቦች ሥፍራቸውን ከሌሎቹ የመጠበቅ የመከላከል ድርጊቶች ነበሩና) መልክና ቅርጽ እያየዘ የመጣው በዚሀ ዘመን ነው ለማለት እጅግ የሚያስቸግርና ምድር በአራቱም ማዕዘናት በሰው ልጆች ከመሞላቷ በኋላም የቀጠለ አሁንም ድረስ ያልተጠናቀቀ ሁልጊዜም አዲስ የቤት ሥራ እየሆነ አንድ ዓይነት መግባባት ላይ ለመድረስ ያልተቻለበት ጉዳይ ነው፡፡ ይሄም ሆኖ ከጥንት ከመሠረት ጀምሮ የሚታወቁ ሀገራት አሉ እንደ ዓለም ታሪክና መንፈሳዊው ተረክ ስናይ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ከተመሠረቱ ህልው ከሆኑ ሦስት ሀገራት አንዷ ናት፡፡ በዚህ ዙሪያ የተለያዩ ተረኮች አሉ፡፡
አንደኛው ኢትዮጵያን የመሠረታት የአዳም ልጅ አሪ ወይም አራም ዓለም በተፈጠረ በ 970ዓመት ነው፡፡ የመጀመሪያ ንጉሷም እሱ ነው እስከ የጥፋት ወኃ ድረስ 21ነገሥታት ነግሠው ለ 1286ዓመታት ኢትዮጵያን ገዝተዋል የሚል ተረክ ለብቻው አለ፡፡ ከጥፋት ውኃ በኋላም ኖኅ ዓለምን ለሦስቱ ልጆቹ ሲያከፋፍል አፍሪካ ለካም ደርሳው ነበርና ኢትዮጵያ ውስጥ ከነገሡት የነገደ ካም ነገሥታት የመጀመሪያው ካም ነው ብለው ከካም የሚጀምሩ አሉ፡፡ አይ አይደለም ከካም ሦስተኛ ትውልድ 2545 ዓመት ቅ.ል.ክ ከሰብታህ ነው የሚጀምረው ብለው ከሰብታህ የሚጀምሩም አሉ፡፡ በዚያም ሆነ በዚህ ሀገሪቱ ጥንታዊትና በሀገር ደረጃ በቀዳሚነት ከተጠሩ ሀገራት አንዷ ናት፡፡ በጥንት የዓለም ታሪክ መጻሕፍትም ሆነ በመንፈሳዊ መጻሕፍት ዛሬ አፍሪካ ብለን የምንጠራውን እንዳለ ኢትዮጵያ ነበር የሚሉት፡፡ በጥንቱ የአውሮፓዊያን የዓለም ካርታ ላይ አትላንቲክ ውቅያኖስን “የኢትዮጵያ ውቅያኖስ” ሲል ይጠራዋል፡፡ በሌላ በኩል ማሊ፣ ቻድ፣ ኒጀር ወደታችም ታንዛኒያ በሌሎች በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራትም ምንጫቸው ኢትዮጵያ እንደሆነ የሚናገሩ በርካታ ማኅበረሰቦች አሉ፡፡ ባሕር ተሻግረን እስክ ቻይና የባሕር ጠረፍ ድረስ እንደገዛንም የዓለም ታሪክ ይናገራል፡፡
ከዚህ ከዚህ የምንረዳው ኢትዮጵያ ምን ያህል ረጅም ታሪክና ሰፊ ግዛት ዕውቅና የነበራት መሆኗን ነው፡፡ ባጠቃላይ ሀገራችን ኢትዮጵያ መጀመሪያ ኩሽ (በካም ልጅ ስም) ዓረቦች ወደ አፍሪካ ከመግቦታቸው በፊት ግብጽ ይኖሩ በነበሩት ጥቁር ሕዝቦች ዘንድ ደግሞ ቶ ኔቶር(ሀገረ እግዝአብሔር) ከዚያ አቢሲኒያ (በንጉሥ አቢስ ስም) ከዚያ ኢትዮጵያ (በንጉሥ ኢትዮጵ ስም) በእነዚህ ስሞች እይተጠራች ኖራለች፡፡ በዚህ እረጂም ጊዜ የቆዳ ስፋቷ ይስፋም ይጥበብ ያልተለወጠ ነገር ቢኖር ማዕከሉ ነው፡፡ የዚህ እጅግ የረጅም ዘመን አገዛዝ ወይም አስተዳደር ዓባይንና ምንጩን ጣናን እንብርት ማዕከል ያረገ ነበርና፡፡ አፍሪካ ኢትዮጵያ ከሚለው የተለየ ስም ለመያዟና አሁን በምናያቸው ሀገራት ብዛት ለመከፋፈሏ አስቀድሞ የዓረቦች ወደ አፍሪካ መግባት ወደ ኋላ ደግሞ የአውሮፓ ቅኝ ገዥዎች ቅርምት ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡
እንግዲህ ኢትዮጵያ እንዲህ እንዲህ እያለች እየጠበበች እየጠበበች መጥታ በከፍተኛ መሥዋዕትነት አሁን ያላትን ገጽታ ብቻ ይዛ ልትገኝ ችላለች፡፡ እንደሚታወቀው ይሄንንም ቢሆን ለማፈራረስና የሀገሪቱን ህልውና ፍጻሜ ላይ ለማድረስ ከውጭና ከውስጥ ምን ያህል እያሰፈሰፉ እያቆበቆቡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
ኢትዮጵያን ለመገንጠል የሚፈልጉ አካላት የፍላጎታቸው መንስኤ ምንድን ነው?
በእኔ እምነት ለዚህ ጥያቄ መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉት ጉዳዮች ሦስት ናቸው
ጭቆናና በደል ይደርስብናል ከሚል ቅሬታ
ከራሳችን አልፎ ለተቀረው የሚተርፍ ሀብት አለን ይሄንን ሀብት ለብቻችን ማድረግ ብንችል የበለጠ ተጠቃሚ እንሆናለን ከሚል የተሳሳተ እምነት
ቅጥረኝነት(ባንዳነት) ሀገርንና ወገንን ከድቶ ለጠላት ጥቅምና ዓላማ ማደር ናቸው፡፡
የእነዚህ መንስኤዎች ተጨባጭነት ምን ያህል ነው?
የመጀመሪያውን መንስኤ ስናይ በእርግጥ በሀገራትን ጭቆናና በደል አልነበረም ማለት ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ተጨባጩና የሚያሳዝነው ነገር ቢኖር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ በብሔረሰብ ደረጃ ተጨቆነ ተበደለ ተረገጠ ተበዘበዘ የሚባል ሕዝብ ካለ የአማራን ሕዝብ ያህል ኢትየጵያ ውስጥ እንዳልነበር ታሪካችንን ስንፈትሽ የአማራ ገበሬ በነገሥታቱ ዘመን ያሳለፈውን ሕይዎት ስናይ የምንረዳው ሀቅ ነው፡፡ የዚህ ምክንያቱ እንደ አለመታደል ሆኖ ሀገሪቱ ከጥንት ጀምሮ ለጦርነት የታደለች ሀገር ከመሆኗ ጋር ተያይዞ የአማራ ሕዝብ ለነገሥታቱ በቅርብ ርቀት ከመገኘቱና ይሄንን የመንግሥት ሥርዓት ከማስቀጠል ኃላፊነትና ግዴታ አንፃር ለሚያጋጥሙ ጦርነቶች ልጆቹን ከመገበር አልፎ ሠራዊቱ ደሞዝ አልባ ነበርና ይህ ሕዝብ ለመንግሥት ከሚሰጠው ግብር በላይ በየመንግሥት ታጣቂው በዘፈቀደ እንደተፈለገ እየተዘረፈ የመመገብ ግዴታን ሲያስተናገድ የነበረ ስለሆነ ነው፡፡
ይህ ድርጊት በሀገራችን ብቻ የነበረ ሳይሆን ተመሳሳይ የመንግሥት ሥርዓት በነበረባቸው ሀገራትም የነበረ ድርጊት ነው፡፡ የአማራው ሕዝብ በዚህ ዓይነት ግዴታ የማለፉ ውጤት አሁን ላይ የኢትዮጵያን ገበሬዎች ሕይወት ተዘዋውረን ስናይ ከሌሎቹ ብሔረሰቦቻችን ይልቅ የአማራ ገበሬዎች ሕይወት እጅግ በሚያሳዝንና ልብን በሚነካ የድህነት ዓይነት የሚኖሩ እንዲሆኑ አድርጓል፡፡ የአማራ ገበሬ በፍጹም ጥሪት መቋጠር የሚችልበትን ዕዳል አግኝቶ አያውቅም ሁለ ነገሩን ለሀገሪቱ ህልውና ለነጻነቱ ከፍሎታል፡፡ ከመኖሪያ ቤቱ አቅም እንኳን ብታዩ የአማራ ገቤሬዎች ቤቶች ከሌሎቹ ብሔረሰቦች ገበሬዎች ቤቶች የደከመና ደሳሳ ነው፡፡ በአንጻሩ የሌሎቹ የደረጀና ጥብቅ አቋም ያለው ሆኗል፡፡ ልብ በሉ እያወራሁ ያለሁት ስለ አማራው ሕዝብ እንጂ ስለ አማራ ነገሥታት አይደለም፡፡ ምንም እንኳን ጥቂቶች የሳቱ የብሔረሰቡ አባላት ብለዋልና ብየ ይህ የመገንጠል ጥያቄ የኦሮሞን ሕዝብ የወክላል ባልልም ለምሳሌ የኦሮሞን ሕዝብ ወይም ገበሬዎች ሕይዎት ብንመለከት ከአማራ በእጅጉ የተሸለ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በቅርቡ በደናቁርት ተሳዳቢ የወያኔ ባለ ሥልጣናት እንደተገለጸው የአማራ ገበሬዎች ሕይዎት እኮ በ 21ኛው መቶ ክፍለ ዘመንም እንኳን ቢሆን ጫማ ለማድረግ ያልታደለ ኅብረተሰብ ነው፡፡ የልብሱም ነገር እንደዚያው ነው፡፡ ምን አለፋቹህ ባጠቃላይ ለዚህች ሀገር እራሱን የሰዋ ሕዝብ ነው፡፡
ታዲያ ለሀገር ሲል በከፈለው ዋጋ ለችጋር መዳረጉ ሊያስመሰግነው እንጂ ሊያስነቅፈው ሊያዘልፈው ይገባ ነበር እንዴ? ለችግር ቢዳረግም ነጻነትን ያህል በምንም ሊገዛ ሊለወጥ የማይችልን ሀብት አትርፏልና፡፡ ይሄ አኩሪ እሴት የአውሮፓ ሀገራት እንኳን የላቸውም አንዱ በሌላው የተገዛ ነውና፡፡ ይህ ሕዝብ በዚህ ትምክህት ያልተሰማው በሌላ በምን ሊመካ ይችላል? ትምክህተኛ ተብሎ መኮነኑ በምን ሒሳብ ነው አግባብነት ሊኖረው የሚችለው? ለነገሩ ያላቸውን ነው ሊሰጡን የሚችሉት የሌላቸውን ከየት ያመጡታል? ሕዝብን በፍቅር ገዝቶና አሳምኖ እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ እንድ ቃል ተናጋሪ በአንድ ሐሳብ አስማምቶ ለልማት እንዲነሣ ማድረጉንማ ከየት አምጥተውት? ችሎታና ሰብእናቸው አይፈቅድላቸውማ? ፍቅርና ክብር አያውቁማ? እንደ እንስሳ ቆጥረው በግዳጅ እያሰለፉ የግብር ውጣ ሥራ ያሠሩ እንጂ፡፡
ከዚህ ባሻገር ስላሉ ነገሮች ስናወራ በሀገራችን በርካታ ብሔረሰቦች የሚያቀርቡት ቅሬታ አለ፡፡ በማንነታችን እንድናፍር እንድንሸማቀቅ እንደረግ ነበር፣ እንደ ዜጋ አንታይም ነበር የሚለው ቅሬታ ወይም በደል አልነበረም አልተፈጸመም ማለት አይቻልም ነገር ግን ምክንያታዊ እንደነበር ልንገነዘብ ይገባል፡፡ በአርግጥ ዛሬ ላይ ሆነን ስናየው ፍጹም አግባብነት የሌለው ሆኖ አናገኘዋልን፡፡ ነገር ግን ይህ ከጥንት ጀምሮ የነበረ ጥቃት እንዴት ሊፈጠር ቻለ? የሚለው ጉዳይ መጤን መመርመር ያለበት ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ ያለ ምክንያት የሚፈጸም ምንም ነገር የለምና አንዴትና ለምን የመገለል እንደ ዜጋ ያለመቆጠር ጥቃት ሊደርስባቸው ቻለ ለሚለው ቅሬታ የኦሮሞን ብሔረሰብ በተመለከተ ወደ 16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወደ ኋላ፤ የትግሬን ብሔረሰብ በተመለከተ ወደ አምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመንና አምስት መቶ ዓመታት ከዚያ ወደኋላ በመመለስ በዚያ ወቅት የነበረውን ሁኔታ ብናየው የዚህ በደል መንስኤ ምን እንደሆነ እንረዳለን፡፡
እንግዳ እቤታችሁ እንዳረፈ አስቡና በእንግደነቱ ሰሞን የሚኖረውን የምትሰጡትን መብት አጢኑት ይህ እንግዳ እቤታችሁ ለዘለቄታው የመቆየት የመኖር ዕድል ቢኖረው ደግሞ ከቤተሰብ አባላት እንደ አንዱ የመቆጠር ዕድል ቢያገኝም ቅሉ በሁሉም ጉዳይ ላይ ግን ልክ ከቤተሰብ አባል አንዱ ሆኖ እንደማይቆጠር እሙን ነው፡፡ ከዚህ አንጻር መሠረታዊ ጉዳዮች በተነሡ ቁጥር የቤቱ ባለቤት “ስንት ለፍቸ ስንት መሥዋዕትነት ከፍዬ ባቀናሁት ቤቴ እኩል ሊገዳደረኝ፣ የባለቤትነት መብቴን ሊጋፋኝ አይገባም” ከሚል አስተሳሰብ የተነሣ እንግደነቱን እንዳይረሳ ለማድረግ፣ እኩል ደራ ደራ ማለቱን ለማቀብ በእንግድነቱ ሊያገኘው ከሚገባው ጥቅም በላይ በቸርነት የተሰጠውን ቤቱን የመጠቀም እንደቤተሰብ የመቆጠር ዕድልን በቂ አድርጎ እንዲያስብ ለማድረግ የተለያዩ ሸንቆጣ ባለቤቱ በእንግዳው ላይ ማድረሱ የማይቀር ይሆናል፡፡ ይህ ሽንቆጣ እንግዳው በእንግድነቱ ዘናትን ባስቆጠረ ቁጥር እንግደነቱ ተረስቶ የቤተሰብ አንዱ አባል እንደሆነ በተቆጠረ ጊዜ ሽንቆጣው ከባድ በደል እንደሆነ ደርጎ የመቆጠር አጋጣሚ ይፈጠራል፡፡ ዛሬ ላይ ተናቅን እንደ ዜጋ አንቆጠርም በማንነታችን እንድናፍር እንድንሸማቀቅ እንደረጋን የሚሉ ወገኖቻችን ይህንን ሁሉ ቅሬታቸውን ዛሬ ላይ አግባብ ሆኖ ብናገኘውም ትላንትና ላይ ግን በፍጹም ሊነሣ አይደለም ሊታሰብ የማይችል ቅሬታ ነበር የእንግድነትን መብት ጠንቅቆ ከመረዳት አንጻር ማለቴ ነው፡፡ እንግዲህ ይህ ሥነ ልቡና ነው እንዲህ ዓይነቱን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት የፈጠረው፡፡ ታሪካዊ ዳራ ምክንያት ሰበብ አለው እንዲሁ ከየትም የመጣ አይደለም ለማለት ነው፡፡ የሆኖ ሆኖ አሁን ላይ በመዋለድም በምንም ባለ መብት ያልሆነ የለምና በደም ተሳስሯልና ቅሬታው አግባብነት ያለውና መቀረፍም ያለበት ነው፡፡
article 39ወደ ሁለተኛው መንስኤ ስንሄድ ላይ ላዩን ስናየውን እንገንጠል ለሚሉት ወገኖች እውነት ሊመስል ይችላል፡፡ ጠለቅ ብለን ስናየው ግን ሀብቱ መኖሩ ስስ እውነት ቢሆንም በተለያዩ የተሳሰሩ ምክንያቶች እንገነጠላለን ባዮችን እንደ ሀገር ህልውና አዝይዞ ለመቀጠል ፍጹም የማያስችል ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ አሁን በምናውቃት ኢትዮጵያ የችኛውም ክልል ተገንጥሎ እንደ ሀገር ህልውና አግኝቶ ለመኖር የሚያስችል አቅም ዕድል ያለው ክልል የለም፡፡ የኢትዮ ኤርትራን ግጭትና ጦርነት የፈጠረውም ጉዳይ ሌላ ምንም ሳይሆን ይሄው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር እኔ በግሌ በተለይ ምሁራን መገንጠልን መፍትሔ አድርገው ያምናሉ ብየ አላስብም፡፡ መገንጠልን መፍትሔ አድርገው የሚያምኑ ምሁራን ካሉ ግን ምሁርነታቸው በጣሙን አጠያያቂ ይሆናል፡፡ እኔ የሚመስለኝ የተማረው ክፍል የመገንጠልን ጥያቄ የሚያንጸባርቀው በመፍትሔነቱ አምኖበት ሳይሆን ለማስፈራራትና በምላሹ መብትን ለማስከበር የመደራደራያ አቅም ለማግኘት፣ ጫና ለመፍጠር ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ዓላማው ለዚህ ቢሆንም እንኳ እልህ ነገሩን ወዳልታሰበ አቅጣጫ ሊወስደው ከመቻሉና ያልተማረውንም ኅብረተሰብ ስለሚያሳስት በማስፈራሪያነትም እንኳን ቢሆን ማንሣቱ ፍጹም ተገቢ ያልሆነና ኃላፊነትም የጎደለው ነው፡፡
ወደ ሦስተኛው መንስኤ ሔድን፡- እንደሚታወቀው ሀገራችን ከጥንት ጀምሮ ዛሬም ድረስ ብዙ ጠላት የሆኑባት ሀገራት ነበሩ አሉም፡፡ ከእነኝህ ሀገራት ጥንተ ጠላት የሆኑቱ ሀገራችን ያለችበት ስልታዊ ቦታና የተፈጥሮ ሀብቷ ህልውናችን ለህልውናቸው አደጋ እንደሆነ በማሰብ ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ጠላት ሲሆኑን፡፡ አዳዲሶቹ ጠላት ሀገራት ደግሞ ከጥቅማቸው ጋራ የዘረኝነት በሽታቸው ተጽእኖ ፈጥሮባቸዋል፡፡ እነዚህኞቹ እንደሰው የማያስቡና ጨካኞችም ናቸው ልክ እነሱ እራሳቸውን ፈለጉት ዘርና የቆዳ ቀለም እንደፈጠሩ ሁሉ ለዚያ የከፋ ጥላቻና ጥቃት ምክንያት ሊሆን የማይችል የማይገባን የቆዳ ቀለምና የዘር ልዩነትን መንስኤ ያደርጋሉና፡፡ የጥቁርን ዘር እንደመገልገያ ዕቃ ቆጥረው ዝንተ ዓለም በቅኝ ግዛት ሲገጥቡት ለመኖር ይፈልጉ የነበሩ ሲሆኑ፤ ሀገራችን ይሄንን ግፈኛ አገዛዝና ኢሰብአዊ ኢፍትሐዊ አስተሳሰብ ከአቅንኦተ ግንኙነት (ዲፕሎማሲ) እስከ ወታደሮቿን በቀጥታ አሰልፋ ቅኝ ግዛትን እንዲያከትምለት ስላደረገች፣ ጥቁር ከነጭ የማያንስ በአንዳንድ ጉዳዮች እንዲያውም የተሻለ የበለጠ መሆኑን በሥልጣኔዋ ማስመስከሯ በጉሮሯቸው ላይ እንደቆመች በመቁጠር ከእርኩሳዊ ቅናትም ጭምር ጥርሳቸውን ነክሰውብን ባጋጠማቸው ዕድል ሁሉ ሲበቀሉን ቆይተዋል ወደፊትም ቢብስባቸው እንጂ ይተውናል ብየ አላስብም፡፡ እንግዲህ እነኝህ ጠላቶቻችን ሁሉም ከድሮ ጀምረው በየራሳቸው ምክንያትና ዓላማ ተሰልፈውብን በየዘመኑ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ሲያጠቁን ኖረዋል፡፡ ለእኛ የከፋብን ግን በተዘዋዋሪ ያደረሱብን ጥቃት ነው፡፡ ምክንያቱም በተዘዋዋሪ የሚደርስብን ጥቃት ዜጎቻችንን በክህደት በማጥመቅ ወደ ባንዳነት ቅጥረኛነት በመለወጥ በመሆኑ ከሚደርሰው ጉዳት በላይ በእነዚህ ዜጎች እንደዚያ መሆን በሀገር ላይ በተለያዩ ምክንያቶች ለዘለቄታው ጥሎት የሚያልፈው የችግርና የጦስ መዘዝ የማይነቀል እሾህ የማይድን ነቀርሳ ይተክላልና ነው፡፡
እዚህ ላይ ወያኔን በምሳሌነት ማንሣት እንችላለን፡፡ ወያኔን ማን አሳድጎ ማን ደግፎ ምን ዓላማ አስይዘው ከቆዳ ቀለማቸውና ከስማቸው በስተቀር ኢትዮጵያዊ ቃና ለዛ ማንነት አልባ አድርገው ቀርጸው ጸረ ኢትዮጵያ አቋም አስታጥቀው ማን ለዚህ እንዳበቃቸው መለስ ብሎ ማጤኑ ለዚህ በቂ ምስክር ነው፡፡ ብዙ ሰው የኪነብጀታ (ቴክኖሎጂ) ውጤት እጅግ ያስደንቀዋል፡፡ እኔን እጅግ የሚገርመኝ የሚደንቀኝ ነገር ግን ጠላቶቻችን ወያኔዎችን እንዴት አድርገው ለምንስ ጥቅም አታለው በገዛ ሀገራቸውና ሕዝባቸው ላይ እንደዚህ ዓይነት ጠላት እንዲሆኑ ማድረግ መቻላቸው ነው፡፡ መታየት ያለበት ከገዥ መደብ አለመሆናቸው አይደለም ይሄ ፈጽሞ እንደምክንያት መወሰድ የለበትም ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ብሔረሰቦች ሁሉ ከ4500 ዓመታት በላይ ለሆነው ታሪኳ፣ ነጻነቷ፣ ሥልጣኔዋ፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እስተዋጽኦ ያላደረገ አንድም ብሔረሰብ የለም፡፡ እንዴትስ ሊኖርስ ይችላል? በመሆኑም የሐገሪቱን ታሪክና ሥልጣኔ የአንድ ብሔረሰብ ብቻ አድርጎ ማሰብ ከቶውንም አይቻልም፡፡ እንዲህ አድርጎ ማሰብ ካልተቻለ በዓለማችን በየትኛውም ሀገር ያሉ ሁሉ ሀገራቸውን ሀገራችን ማለት ባልቻሉ ነበር፡፡
በየትኛውም ሀገር ብንሔድ ለየሀገሩ ሥልጣኔና ህልውና የአንዱ ብሔረሰብ አስተዋጽኦ ጎልቶ መታየቱ አይቀርም እንዲህ በመሆኑ ግን ሌሎቹ ሀገሪቱንና አጠቃላይ እሴቷን የኛ አይደለም እንዲሉ አላደረገም፡፡ በአንዱም ባይሆን በሌላው በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ለዚያች ሀገር አስተዋጽኦ ማድረጋቸው አይቀርምና፡፡ በመሆኑም ሀገሪቱ ሀገራቸው ናት ታሪኳም ታሪካቸው ነው፡፡ እውነታው እንዲህ በሆነበት ሁኔታ ሰው እንዴት በገዛ ሀገሩ ታሪክ፣ ሥልጣኔ፣ ሉዓላዊነት፣ መለያ፣ ማንነት፣ ክብር፣ እሴት፣ ሀብት ላይ የጥፋት ሰይፍ ታጥቆ ይዘምታል? ጥቅማቸውና ትርፋቸውስ ምንድን ነው? ለዜጎች ከሀገራቸው የበለጠ ጥቅም ዋጋ ክብር ትርፍ ምን ነገር ኖሮ ለዚያ ሊጓጉ ሊቋምጡ ሊታለሉ ቻሉ? ለማንኛውም ጠላቶቻችን ይሄንን ያህል ተሳክቶላቸዋል፡፡ እጣ ፋንታችንም በመዳፋቸው ውስጥ እንደሆነ ያስባሉ ልክ ገመዱን በአንገታችን ላይ እንዳጠለቁና ገመዱን ሸምቅቀው ለህልፈት የማብቃትና ያለማብቃት ጉዳይ በእነሱ ፍላጎት እንደሚወሰንም፡፡ እውን ግን እንደዚያ ይሆን ይሆን?
የመገንጠልን ጥያቄ አግባብነት የሚያሳጡ አመክንዮዎች?
በሀገራችን ችግሮች አሉ ተብሎ መገንጠልን በመፍትሔነት መውሰድና ለመውሰድ መሞከሩ ፍጹም አግባብነት አይኖረውም፡፡ መገንጠል በምንም ተአምር መፍትሔ ሊሆን አይችልም አግተልትሎ የሚያስከትላቸው በርካታ ጥያቄዎች አሉና፡፡ ብቸኛው መፍትሔ በደሉ ቅሬታው ችግሩ እንዲቀር እንዲወገድ ለማድረግ ፍትሕ እኩልነት እንዲሰፍን መታገል ብቻና ብቻ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ያለ የኢትዮጵያ ሕዝብ አካል የሆነ ሕዝብ የመገንጠል መብት ሊኖረው የማይችልበት አምስት ዐበይት ምክንያቶች አሉ፡፡
መግቢያችን ላይ ስለ ሀገር ትርጉም ባብራራንበት ወቅት ሀገር በጋራ የሚኖርባት ትልቅ ቤት ነች ማለታችን ይታሳል፡፡ በመሆኑም የዚያ ቤት መፍረስ በየትኛውም ጫፍ ላለ የዚያ ቤት ነዋሪ በቀጥታ ይመለከታዋል ይገደዋል ማለት ነው እንጂ ገንጣዩ ያለበትን አንድ ጫፍ አፍርሼ እወስዳለሁ ስለለ ጉዳዩ የሱ ብቻ ተደርጎ ሊወሰድ አይችልም፡፡ ቤቱ የፈረሰው በአንድ ጫፍ በኩል ይሁን እንጂ የቤቱ መፍረስ በሌላኛው ጫፍ ላለው የቤቱ ነዋሪ ጉዳትና አደጋ ማድረሱ አይቀርምና፣ ሀገሬ ብሎ እዚያ ድረስ እየዘመተ በትውልድ ሁሉ ዋጋ ሲከፍል ኖሯልና፣ መሥዋዕት ሆኗልና፣ ከእነሱ አንዱ የዚያች ሀገር (የጋራ ቤት) ሕዝብ አካል የነበረ ብሔረሰብ መገንጠል ቢፈልግ ሌሎቹ ወይም ከፊሎቹ የማይፈልጉ ይሆናሉና፣ በዚህ ሰዓት በአንድም ወይም በሌላ አጋጣሚ የመገንጠሉ ዓላማ ቢሳካም እንኳ ግጭቱን ወይም ችግሩን ወደ ሌላ ዓይነት የቀውስ ዙር መለወጥ እንጅ የሰላም መፍትሔ ሆኖ አናገኝውምና፣ መገንጠሉን የማይፈልገው ቡድን የተገነጠለውን የሀገሩን ክፍል ለመመለስ መዋጋቱ አይቀርምና፣ የአንድ ጫፍ መፍረስ ከነአካቴውም ለአጠቃላዩ የቤት መፍረስ መንስኤ ይሆናልና በእነዚህ ምክንያቶች አንዱ ሌሎቹን አያገባችሁም ውሳኔው የግሌ ነው ሊል አይችልም ማለት ነው፡፡ በዚያ ቤት ጉዳይ ላይ ሁሉም ነዋሪዎች ይመለከታቸዋል ማለት ነው፡፡ ያ ቤት ለመገንባቱ የሁሉም አስተዋጽኦ ሊኖርበት ግድ እንዳለ ሁሉ በሌላው ጉዳይም እንዲሁ እኩል ይመለከታቸዋል፡፡
በየትኛውም መመዘኛ ቢሆን እራስን ማጥፋት መፍትሔ አይደለም፡፡ ሀገር መገነጣጠል እራስን እንደማጥፋት ይቆጠራል፡፡ ሰው መቸም ካልታመመ የአእምሮ ጤናውን ካላጣ በስተቀር እራሱን አያጠፋም ካልታመመ የአእምሮ ጤናውን ካላጣ በስተቀር እራሱን አያጠፋም፡፡ በመሆኑም ሀገርን እንገነጣጥል የሚሉ አካላት ጤናም እንዲሁ ነውና መብት ሊሆን አይችልም፡፡ ራስን ማጥፋት ወንጀል ነው ወንጀልነቱ እራሱን ለሚያጠፋው ብቻ ሳይሆን እራሱን ሲያጠፋ በዝምታ ለሚመለከተውም ጭምር ነው፡፡ ስለሆነም የአእምሮ ጤና የተጓደለባቸውን ወገኖች ይሁንላችሁ እንዳሻችሁ ልንል አይቻለንም፡፡
በአንድ ወቅት ያለ ሕዝብ በሌላ ወቅት የሚመጣን ሕዝብ መወከል ስለማይችል በእጣ ፋንታውም ላይ መደራደር አይችልም ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም የውክልናውን የአግባብነት ጉዳይ ጥያቄ ስለሚያስነሣ፡፡ በአካል የሌለ ግን የሚመጣ ሕዝብ አሁን ያለን ሕዝብ መወከልም ስለማይችል፡፡ አሁን ያለውም አሁን በሌለው ግን በሚመጣው ሕዝብ መወከል ስለማይችል፡፡ ይሄ በሆነበት ሁኔታ ሁለቱም አካላት እኩል መብት አላቸውና አንደኛው በሌላኛው እጣ ፋንታ ላይ እውቅናና ውክልና ባልተሰጣጣበት ሁኔታ ሊወስንበት አይችልም መብት የለውም፡፡ ይህንና መሰል ጉዳዮችን በተመለከተ የየትኛውም ትውልድ መብቱ የሚሆነው የነበረውን ጠብቆ ተንከባክቦ የተቀበለውን እሱም የማስተላለፍ ብቻ ነው፡፡ እሴት መቀነስ አይችልም መጨመር እንጂ፡፡
የመገንጠል ጥያቄ መልስ መገንጠል በፈለገው አካባቢ በሚኖረው ሕዝብ ፍላጎት ከተወሰነና መብት እንደሆነ ከታመነ “ከዚህ በፊት ማንዴላ በሚለው ግጥሜ ላይ እንደገለጽኩት” ለኔ ለብቻዬ የሚለው ጥያቄ የመጨረሻ ማቆሚያ ግለሰብ ላይ ይሆናል እንጅ ብሔረሰብ ላይ ብቻ የሚቆም አይሆንም፡፡ ሀገሪቱ ከ 80 በላይ ብሔረሰብ አላትና ከሰማኒያ ብቻ ተቆራርጣ የምትቀር አይሆንም፡፡ በአሁኑ ወቅት በሀገራችን የተለያዩ ስፍራዎች በጎሳዎች መካከል በግጦሽ መሬትና በውኃ ሳቢያ የኔ ነው የኔ በመባባል እየተጋጨ አየተጫረሰ እንደምናየው የኔ የብቻዬ የሚለው ጥያቄ ወደ ጎሳም ይወርዳል ከጎሳም ወደ ንኡስ ጎሳ ከንዑስ ወደ ንዑስ እያለ ወደ አባወራ ይወርዳል፡፡ በመሆኑም አስተሳሰቡ ከቀላል ችግር ወደ ካባድና ወደ ሰፊ ችግር የሚከት እንጂ መፍትሔና ሰላምን የሚሰጥ አይደለም፡፡ እናም አስተሳሰቡ የተሳሳተ ብስለት የጎደለው የሰው ልጅን የሠለጠነ አስተሳሰብ ወደ ኋላ የሚመልስ ኋላ ቀር አስተሳሰብ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ መግቢያዬ ላይ እንዳልኩት ሀገርን የፈጠራት ሰፊ ፍላጎትና የአቅም ማደግ ነው ብለናልና፡፡
ነባራዊ ሁኔታ ነው፡፡ ምን ማለቴ ነው እገነጣላለሁ የሚለው አካል ማንነት ጉዳይ ነው፡፡ እገነጠላለሁ የሚለው አካል ማንም ቢሆን የመገንጠል ዕድሉ ይሰፋል ማለቴ ሳይሆን በተለይም ደግሞ እገነጠላለሁ የሚለው ብሔረሰብ የኋላ ታሪክ ሲታይ ለዚያች ሀገር እንግዳ ወይም ባዕድ ከሆነ ሁኔታው አስገራሚ ገጽታ ይኖረዋል፡፡ ለምሳሌ ይህንን ጉዳይ በሀገራችን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ብናይ ኢትዮጵያ ውስጥ የመገንጠል ጥያቄ ያነሡትን እራሳቸውን የኦሮሞ ብሔረሰብ ተወካይ አድርገው የሚጠሩትን ኦነግን ብናይ የራስን ታሪክ ጠንቅቆ ካለማወቅ ካልሆነ በስተቀር የኦሮሞ ሕዝብ ለኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ እንግዳ ሕዝብ እንደሆኑ እያወቁ ይኘየንን ጥያቄ ማንሣት እጅግ የዋህነት ነው ልክ ሊሆኑና ጤነኞችም ሊያሰኛቸው የሚችለው ባለቤት አልባ መሬት ቢሆን ነበር፡፡ በመሆኑም ይሀንን ጥያቄ ማንሣቱ አግባብነት አይኖረውም ማለት ነው፡፡
በእነዚህ አምስት ነጥቦች ምክንያት ኢትዮጵያ ውስጥ የመገንጠል ጥያቄን ማስተናገድ ከቶውንም አይቻልም ድርጊቱም መፍትሔ ሳይሆን ጥፋት ነው፡፡
የወያኔ ሕገ መንግሥትና የመገንጠል ጥያቄ
ያደጉ ሀገራት ሕገ መንግሥታት ለምሳሌ የዩ.ኤስ. አሜሪካን ሕገ መንግሥት ያየን እንደሆነ እነኝህን ከላይ የጠቅስናቸውን አምስት ነጥቦች በቅጡ የተረዳ ይመስላል፡፡ ምክንያቱም ስለ ሉዓላዊ ሥልጣን ሲናገር ያውም በሀገሪቱ ላይ ሳይሆን በሕገ መንግሥቱ ላይ ነው “ሕገ መንግሥቱ የተመሠረተው በሕዝቡ በመሆኑ ሉዓላዊነቱም የሕዝቡ እንጂ የነገድ፣ የጎሳ ወይም የሃይማኖት ቡድኖች አይደለም” ይላል ፡፡ ልብ በሉ ሉዓላዊ ሥልጣን አንድ ሕጋዊ ሰውነት ያለው የአጠቃላይ የአሜሪካ ሕዝብ ነው አለ እንጂ በነገድ በጎሳ ስም የተለያየ ህልውና ላላቸው አካላት አላደረገም፡፡ ያውም በሕገ መንግሥቱ ላይ እንጅ በሀገሪቱ ላይ በእጣ ፈንታዋ ላይ ለመወሰን ዕድልና ክፍተት አልሰጠም ምን ያህል ጥንያቄ እንዳደረገ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ወደ ወያኔ ሕገ መንግሥት ስንመጣ ግን እጅግ በሚገርምና በሚያሳዝን መልኩ ነገሮችን ጠልቆና ረቆ ያለመረዳት ችግር ያለበት ግልብነትና እንጭጭነት ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡
ሁሉም ሉዓላዊ ሥልጣን በኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ውስጥ ይሆናል በማለት የብሐረብሔረሰቦችን መብት እስከ መገንጠል ድረስ ነው በማለት የሀገሪቱን ህልውና አደጋ ላይ በመጣልና ለማፍረስ በማሴር ተጀምሮ እስኪጨርስ የሚያወራው ብሐር ብሔረሰቦች እያለ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ አንድ ሀገር ሕዝብ ሕዝብ ተብሎ በወል የሚያስጠራውን ለሀገሩ ያለውን የጋራ የሀሳብ አንድነት አፈራርሶ ሕዝቦች በማለት አንድ ሀሳብና ፍላጎት ለአንድ ሀገር እንደሌላቸው ወይም እንዳይኖራቸው አድርጓል፡፡ ከዚህም በላይ ሀገርን በርእሰ ጉዳይ አንሥቶ ዕውቅና እንኳን ለመስጠት ሀገራችን ብሎ ስለሀገር ለማውራት የተሳነው የሞራል (የቅስም) ብቃትና ድፍረት የጎደለው ቁንጽል ደካማና ባዕድ ሕገ መንግሥት ነው፡፡
በአንድ በኩል የዚህ አስተሳሰብ መሠረት የወያኔ ባልሥልጣናት በተለያዬ ጊዜ ሲገልጹ እንደተደመጡት “የብሔር ብሔረሰቦች መብት እስከመገንጠል የሚለው መብት የተቀመጠው የብሔር ብሔረሰቦች መብት የት ድረስ እንደሆነ ለማሳየት እንጂ እንዲገነጣጠሉ ለማድረግ አይደለም፡፡ መብታቸው እስከተከበረላቸው ጊዜ ድረስ ይሄንን የመገንጠል ጥያቄ የሚያነሣ አይኖርምና መብታቸውን የሚነፍግ ሁኔታ ካጋጠመ ግን ዋስትናቸው ሕገ መንግሥቱ ነው በዚያ መሠረት የመሰላቸውን የመወሰን መብት አላቸው” ይላሉ እነ አቶ መለስ ያልተረዱት ያልገባቸው ነገር ቢኖር አንድ ብሔረሰብ የመገንጠል ጥያቄ ሊያነሣ የሚችለው መብቱና እኩልነቱ ካልተረጋገጠለት ብቻ አለመሆኑን ነው፡፡ መብታቸው ያለ እንከን ቢጠበቅላቸውም እንኳን ይህ የመገንጠል ጥያቄ ሊነሣ መቻሉን ነው፡፡ ለምሳሌ በአንዳንድ ሀገራት ላይ እንደተስተዋለው ሀብት ያለው የተወሰነው የሀገሪቱ ክፍል በመሳሳትና የተሻለ የሕዝባዊ ኑሮ እድገት ላሉበት ለሚኖሩበት የራሳችን ለሚሉት በዚያ አካባቢ ላለ ሕዝብ በመመኘት ከተቀረው የሀገሪቱ ከፍል መገንጠልን የሚፈልጉበት አጋጣሚ በተደጋጋሚ ነዳጅና የከበሩ መአድናት በተገኙባቸው የሌሎች ሀገራት የተለያዩ ቦታዎች የተከሰቱ ጉዳዮች አሉ፡፡ ልዩነትን ካላቻቻሉት በስተቀር መፈጠሩን ማቆም አይቻልም ይህ ገሀዳዊ እውነታ ነው፡፡ እንኳን በሀገር ማለት በጋርዮሽ ውስጥ ይቅርና በአንድ ሰው ውስጥ እንኳን ይፈጠራል ሰው ከራሱ ጋር መግባባት የሚሳነው ጊዜ በርካታ ነውና፡፡ ልዩነት ተፈጥሯዊ ነው፡፡ ይሄንን መግታት ከቶውንም አይቻልም፡፡ ማድረግ የሚቻለው ማቻቻል ነው፡፡
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
የወያኔ ሕገመንግሥት ይሄንን ሀቅ መገንዘብ አልቻለም፡፡ ያውም እኮ ላያደርጉት ነው፡፡ እንግዲህ ለዚህ ነው ልዩነት በተፈጠረ ቁጥር ውሳኔው ያንተ ነው መባል አለበት የሚለው አስተሳሰብ ያልበሰለ ነው ይምለው፡፡ እናም የወያኔ ሕገ መንግሥት የአመለካከት አድማሱ በጣም የጠበበ ግራ ቀኝ የማያማትር ከአድማስ ትዕይንት(scenery) ጀርባ ስለሚኖረውና ስላለው ነገር ሁሉ ምንም የሚያውቀው ነገር የሌለው እንዳለም የማይረዳ ደካማ ሕገ መንግሥት ነው፡፡ እንዲያው ነገሩን አልኩ እንጂ ሕገ መንግሥታቸው የብሔር ብሔረሰቦች መብት እያለ ይደስኩር እንጂ የተባሉት መብቶቻቸው ለአንድም ቀን ቢሆን ተከብሮ አያውቅም፡፡ ወያኔ ህልውናውን የመሠረተውና ያረጋገጠው የእነሱን መብት በመንፈግና እነርሱን ጠርፎ በማሰር ላይ ነውና፡፡ ስለ እውነት ለመናገር ሳንወድ በግድ ቢሆንም ሀገሬ እንዲህ ዓይነት ሕገ መንግሥት እንዲኖራት ስለተደረገች እንዴት ሀፍረትና ውርደት ይሰማኛል መሰላችሁ፡፡
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
የወያኔን ከፋፋይ አገዛዝ እናምክን!!!
የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰብ ሊከበርላቸውና ሊያሳድጋቸው የሚገቡ የተለያዩ የባህልና የታሪክ ቅርሶች ያሏቸውን ያህል በብዙ መንገድ የሚያይዝ የጋራ ታሪክ ቅርስና ዝምድና አላቸው። ልዩነቶቹ ራሳቸው ተጠቃቃሚ ለሆነ የእርስበርስ ግንኙነታቸው ጠቃሚ እንጂ ከአንድ ሀገር ማህበረሰብነታቸውና ከጋራ ህልማቸው ጋር የሚጋጩ የጠብና የግጭት መንስኤዎች አይደሉም። ከጠብና ግጭት ማንኛውም ብሄር ብሄረሰብ ተጠቃሚ አይደለም። ከጠብና ግጭት ጥቅም ይገኛል ብለው የሚያስቡ “ግርግር ለሌባ ይመቻል” የሚለውን የወሮ በላ ፍልስፍና የሚከተሉ የቀን ጅቦች እንጂ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች አይደሉም። በወያኔ የግዛት ዘመን የደረሱትን ግጭቶች መፈናቅሎችና የተፈጠሩትን የእርስበርስ ጥርጣሬዎችን ልብ ብሎ ለተመለከተ ሁሉም በአገዛዙ እና በሎሌ የበታች ሹማምንቱ የተፈጠሩ እንጂ አንድም ጊዜ እንኳን ከህዝብ የመነጩ አይደሉም።
የወያኔ ጉጅሌ በአገዛዝ ዘመኑ ሁሉ ብሄር ብሄረሰቦችን ከሚያይዟቸው የጋራ ማህበራዊ ቅርሶችና ህልሞች ይልቅ ካለመታከት ልዩነቶቻችን ላይ ያተኮረ ፖለቲካ እያካሄደ እንዳለ ግልጽ ነው። ከዚህ አልፎም አዳዲስ የእርስበርስ ግጭቶችን እና ጠቦች እንዲፈጠሩ ተግቶ የሚሰራ ከፋፋይ ቡድን ነው። እርስበርሱ መጠራጠርና መፈራራት እንዲሰፍን ልዩ ልዩ ስልቶችን ይቀይሳል። ከአንዱ ብሄረሰብ ተንኳሽ አዘጋጅቶ ሌላው ብሄረሰብ ላይ አደጋ እንዲደርስ ከዚያም ተጠቃሁ የሚለው አጸፋ እንዲመልስ ያደርጋል። የአንዱን ብሄረሰብ መንደርና ንeበረት በእሳት ለኩሶ በሌላው ብሄረሰብ እንዲመካኝ ያድርጋል። አንዱ በአንዱ ላይ እንዲያማርር ከንፈሩን እንዲነክስ ማድረግ ለወያኔ ጉጅሌዎችና ለሎሌዎቻቸው እንደፖለቲካ ጥበብ ከታየ ሁለት አስርት አመታት አልፈዋል። በየትኛውም የሀገራችን አካባቢዎች የተቀሰቀሱ የርስበርስ ጥርጣሬዎችና ግጭቶችን ያሸተተ ሁሉ ወያኔ፣ ወያኔ እንደሚገሙ ያረጋገጠው ጉዳይ ነው።
ወያኔዎች የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች ከፋፍለውና ከቻሉም አጋጭተው ካልሆነ በስተቀር የዝርፊየ ኢኮኖሚያቸውን መቀጠል እንደማይችሉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች የጋራ ጥቅማቸውንና ህልማቸውን ይዘው የተነሱ እለት ወያኔ ያከተመለት መሆኑን ያውቃል። ለዚህም ነው በየክልሉ እና ዞኑ በፍጹም ከሆዳቸውና ጥቅማቸው በላይ ማሰብ የማይችሉ ግለሰቦችን ከየብሄረሰቡ እየመረጠ የሚሾምልን። ወያኔ ነጻ የህዝብ ምርጫ የሚፈራው ለዚህ ማረጋገጫ ነው፡፡
የወያኔ ጉጅሌዎች ከጊዚያዊ ጥቅም በዘለለ ማሰብ ስለተሳናቸው እንጂ ይህ አካሄዳቸው ለራሳቸውም ለዘለቄታው የማይጠቅም መሆኑን ዘንግተውታል። በልዩነታችን ላይ መጫወት ማለት በእሳት እንደ መጫወት የማይመስላቸው ለዚህም ነው። ይህ የተጀመረው እሳት ራሳቸውንም አይምርም።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
Subscribe to:
Posts (Atom)